መጋቢት 2 ቀን 2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ
የጤፍ ገበያ ማረጋጊያ ሥራ
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የእህልና ቡና ንግድ ሥራ ዘርፍ በአሁኑ ወቅት የተፈጠረውንና የሚታየውን ከፍተኛ የጤፍ ዋጋ ንረትን ለማረጋጋት፡-
ከዚህ በተጨማሪ
የፓልም ምግብ ዘይት ከንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በተሰጠው ኮታ መሰረት ለአዲስ አበባ፣ ለአማራ፣ ለሱማሌ፣ ለድሬዳዋ፣ ለሐረር፣ ለደቡብ ምዕራብ እና ጋምቤላ ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች በአዲስ አበባ የምርት ማሠራጫ ዋጋ
ባለ 3 ሊትር ብር 314
ባለ 5 ሊትር ብር 510
ባለ 20 ሊትር ብር 2,003
በጄሪካን ሂሳብ መነሻ እንደሁኔታው የትራንስፖርት ሂሳብ ታክሎ በህብረት ሥራ ዩኒየኖች አማካይነት በማሠራጨት ገበያውን በማረጋጋት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ አድርጓል፡፡
--//--
የፕሬስ መግለጫ
የካቲት 10 ቀን 2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ2015 ግማሽ ዓመት አፈጻጸም 2,036,415 ኩንታል የመሰረታዊ ፍጆታ ምርት ለገበያ አቀረበ
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ2015 በጀት ዓመት ስድስት ወራት 2,036,415 ኩንታል የመሰረታዊ ፍጆታ ምርት ለገበያ አቀረበ፡፡ ኮርፖሬሽኑ ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታውን ግምት ውስጥ በማስገባት በግማሽ ዓመቱ ለገበያ ላቀረበው ምርት ብር 5,900,116,922 ወጭ በማድረግ የዕቅዱን በመጠን 111 በመቶ በዋጋ ደግሞ 98 በመቶ አከናውኗል፡፡ ከተገኘው ጠቅላላ ሽያጭ ገቢ 93.1 በመቶ ከሀገር ውስጥ ሽያጭ ገቢ የተገኘ ሲሆን ቀሪው 6.9 በመቶ ከኤክስፖርት የተገኘ ገቢ ነው፡፡ የግማሽ ዓመቱ አጠቃላይ ሽያጭ መጠን ከ2014 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ሽያጭ ጋር ሲነፃፀር 41 በመቶ ብልጫ አለው፡፡
ኮርፖሬሽኑ በ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት በመሠረታዊ የፍጆታ ምርት ብር 2,452,146,728 ዋጋ ያለው 590,075 ኩንታል ምርት በሃገር ውስጥ ገዝቶ ለማቅረብ አቅዶ የነበረ ሲሆን በዚህ ወቅት በብር 1,693,176,828 ዋጋ ያለው 764,606 ኩንታል ግዢ አከናውኗል፡፡ የኮርፖሬሽኑ የሀገር ውስጥ ግዥ በመጠን ከ2014 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ግዥ ጋር ሲነፃፀር 62 በመቶ ብልጫ አለው፡፡
የሀገር ውስጥ የፍጆታ ምርቶችን ለተጠቃሚው ከማሰራጨት አንጻር የተከናወነውን በተመለከተ ባለፈው ዓመት ተገዝቶ ሳይሸጥ የተላለፈውን ጨምሮ ለሀገር ውስጥ ገበያ ኮርፖሬሽኑ ብር 3,273,864,897 ቢሊዮን ዋጋ ያለው 999,481 ኩንታል ምርት ስርጭት አከናውኗል፡፡ የመሰረታዊ ፍጆታ ምርት ስርጭት አፈፃፀም ከ2014 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 5 በመቶ ብልጫ አለው፡፡
በሀገር ውስጥ የፍጆታ ምርቶች ግብይት ሽያጭ ኮርፖሬሽኑ ያገኘው ገቢ ብር 5,822,656,134 ሲሆን ይህም በገቢ ድርሻ እህልና ቡና 65.4 በመቶ፣ የምግብ ዘይት ስርጭት 16.3 በመቶ፣ ስኳር 2.8 በመቶ፣ የኮንስትራክሽን ግብአቶች 7.2 በመቶ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ሥርጭት 2.5 በመቶ በድምሩ 94.1 በመቶ ድርሻ ሲኖራቸው ቀሪው 5.9 በመቶ የሌሎች ፋብሪካ ምርቶችና አገልግሎት ሽያጭ ገቢ ድርሻ ነው፡፡
የውጭ ሀገር ሽያጭ አፈፃፀምን በተመለከተ ኮርፖሬሽኑ በ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ለውጭ ገበያ 6,577 ኩንታል የተለያዩ የብርዕ፣ ጥራጥሬ፣ የቅባት እህሎች፣ ቡና እና ፍራፍሬ በብር 77,460,788 ሽያጭ አከናውኗል፡፡ በግማሽ ዓመቱ ኤክስፖርት ከተደረገው ምርት ሽያጭ 1,484,418.70 የአሜሪካን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡
ገበያን ለማረጋጋት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት
ኮርፖሬሽኑ በተለያዩ አካባቢዎች የተመረቱ መሰረታዊ የፍጆታ ምርቶችን አምራቹን በሚያበረታታ የመግዣ ዋጋ ገዝቶ በማቅረብ ተጠቃሚው ህብረተሰብ በአቅርቦት እጥረትና በገበያ ዋጋ መናር እንዳይጎዳ በቂ ምርት ካለበት እጥረት ወዳለበት በማጓጓዝና በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያውን በማረጋጋት ኮርፖሬሽኑ በርካታ ስራዎች አከናውኗል፡፡
ኮርፖሬሽኑ የምርት አቅርቦት እጥረትንና የዋጋ ንረትን ለመከላከልና ገበያውን ለማረጋጋት ቅድሚያ ለሚሰጣቸው ተቋማት ለዳቦ ቤቶች፣ ለዱቄት ማምረቻ ፋብሪካዎች ለሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ ለአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን፣ ለፌደራል ፖሊስ፣ ለማረሚያ ቤቶች 1,099,764 ኩንታል ስንዴ ሽያጭ አከናውኗል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በሀገሪቱ የገጠመውን የምርት አቅርቦት እጥረት ለመሸፈን በተለይም በዓለም ምግብ ድርጅት በኩል ለዕርዳታ የሚሰራጭና ለሃገር ውስጥ የዱቄት ፋብሪካዎች ብር 469,033,548 ዋጋ ያለው 163,389 ኩንታል በቆሎ፣ ለመንግሥት ሠራተኛው፣ ለማረሚያ ቤቶችና ሌሎች ሸማች የህብረተሰብ ክፍሎች ብር 50,126,519 ዋጋ ያለው 11,308 ኩንታል ጤፍ፣ ብር 148,726,857 ዋጋ ያለው 34,306 ኩንታል ፍራፍሬና አትክልት፣ ብር 945,114,745 ዋጋ ያለው 7,501,100 ሊትር የምግብ ዘይት፣ ብር 164,608,416 ዋጋ ያለው 38,754 ኩንታል ስኳር፣ ብር 174,300,051 ዋጋ ያለው 23,543 ኩንታል ልዩ ልዩ የፍጆታ ሸቀጦች ለህብረተሰቡ በማሰራጨት ለተጠቃሚው ህብረተሰብ የገበያ ዋጋ ለማረጋጋት ጥረት ተደርጓል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም በግንባታው ዘርፍ እየገጠመ ያለውን ከፍተኛ የሆነ የሲሚንቶ አቅርቦት እጥረትና ዋጋ መናር ለመከላከል ከፋብሪካዎች 431,266,075 ዋጋ ያለው 549,701 ኩንታል በቀጥታ በመረከብ ለተጠቃሚው በተመጣጣኝ ዋጋ ማሠራጨት ተችሏል፡፡
የኮርፖሬሽኑ መሰረታዊ ፍጆታ ምርቶች መሸጫ ዋጋ ከነፃ ገበያ ዋጋ ጋር ንጽጽር
ጤፍ
ነጭ ጤፍ በኩንታል የገበያ ዋጋው 5‚700-6‚000 ሲሆን በኮርፖሬሽኑ 4‚700 ብር ይሸጣል ይህም ከ21-25 በመቶ የዋጋ ቅናሽ አለው፡፡ ሰርገኛ ጤፍ ከብር 5‚200 እስከ 5‚500 በገበያ ዋጋ እየተሸጠ ሲሆን የኮርፖሬሽኑ የመሸጫ ዋጋ ብር 3‚960 ነው በዚህም ከ24-25 በመቶ የዋጋ ልዩነት አለው፡፡ ቀይ ጤፍ ከብር 4‚250 እስከ 4‚310 በገበያ ዋጋ እየተሸጠ ሲሆን የኮርፖሬሽኑ የመሸጫ ዋጋ ብር 3‚200 ነው፡፡ በዚህም ከ24.7-25.8 በመቶ የዋጋ ልዩነት አለው፡፡
ስኳር
ስኳር በኪሎ ግራም ከብር 73.50 እስከ ብር 120 ብር ገበያ ላይ እየተሸጠ ሲሆን በኮርፖሬሽኑ 57.00 ብር እየተሸጠ በመሆኑ ከ42-65 በመቶ የዋጋ ቅናሽ አለው፡፡
ፓልም የምግብ ዘይት
ባለ 3 ሊትር ከብር 450-498፤ ባለ 5 ሊትር ከብር 700-800፤ ባለ 20 ሊትር ከብር 2,700-3,040 በገበያ ላይእየተሸጠ ሲሆን በኮርፖሬሽኑ በቅደም ተከተል ሶስት ሊትር በብር 314 አምስት ሊትር ብር 510 ሃያ ሊትር ብር 2‚003 የሚሸጥ በመሆኑ 25-36 በመቶ ልዩነት አለው፡፡
ፓስታ እና ማካሮኒ
ፓስታ እና ማካሮኒ የገበያ ዋጋቸው በኪሎግራም ፓስታ ከብር 45-50 መኮሮኒ ከብር 65-67 ሲሆን በኮርፖሬሽኑ የገበያ ዋጋቸው ፓስታ ብር 37 መኮሮኒ ብር 63 በመሆኑ በፓስታ 17-26 በመኮሮኒ 3-6 በመቶ የዋጋ ልዩነት አላቸው፡፡
የስንዴ/ዳቦ ዱቄት
የስንዴ/ዳቦ ዱቄት የገበያ ዋጋው በኩንታል ከብር 6,320 እስከ 6,575 ሲሆን የኮርፖሬሽኑ መሸጫ ዋጋ ብር 6,135 በመሆኑ ከ2.9%-6.7% የዋጋ ልዩነት አለው፡፡
ሙዝ እና ብርቱካን
ሙዝ የገበያ ዋጋው በኪሎግራም 50-60 ብር ብርቱካን 140-150 ብር ሲሆን በኮርፖሬሽኑ የገበያ ዋጋቸው ሙዝ 40 ብር ብርቱካን 60 በመሆኑ በሙዝ 20-33 ብርቱካን 57-60 በመቶ የዋጋ ልዩነት አለው፡፡
ሲሚንቶ
በኩንታል 1,450-1,550 የሚሸጥ ሲሆን ሙገር 723 እና ዳንጎቴ 807.87 የሚሸጥ በመሆኑ 46.7-53.9 በመቶ የዋጋ ልዩነት አለው፡፡
--//--
ለተጨማሪ መረጃ +251 114 166441 ይደውሉ፡፡