GridArt_20231012_110101692.jpg

የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ በተሟላ ሁኔታ ለመፈፀም ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራ ላይ ይገኛል፡፡ ከምርት ግዥና ሽያጭ ጋር በተያያዘ ኮርፖሬሽኑ በነሐሴ ወር በሀገር ውስጥ እና በኤክስፖርት ገበያ ለመሸጥ ያቀደው የእህል፣ ቡና፣ የፍጆታ ዕቃ እና አትክልት እና ፍራፍሬ ምርት መጠን 89 ሺህ ኩንታል በብር 556.4 ሚሊዮን ሲሆን 164.8 ሺህ ኩንታል በብር 925.1 ሚሊዮን በመሸጥ ዕቅዱን በመጠን 185 በመቶ እንዲሁም በዋጋ 166 በመቶ አከናውኗል፡፡

 

በአጠቃላይ በነሐሴ ወር በሀገር ውስጥ 45.2 ሺህ ኩንታል እህል፣ ቡና፣ ሲሚንቶና የምግብ ዘይት በብር 217.8 ሚሊዮን ለመሸጥ ዕቅድ ተይዞ 123.9 ሺህ ኩንታል እህል፣ ቡና፤ ሲሚንቶና የምግብ ዘይት በብር 556.52 ሚሊዮን በመሸጥ በመጠን 276 በመቶ፤ በዋጋ 255 በመቶ ለማከናወን ተችሏል፡፡ በተጨማሪም በወሩ ውስጥ 576 ኩንታል ቡና በብር 16,758,720 ኤክስፖርት በማድረግ ገቢ ተገኝቷል፡፡

 

ኮርፖሬሽኑ በነሐሴ ወር ላይ ለመሸጥ ያቀደው የአትክልትና ፍራፍሬ እና የፍጆታ ምርቶች መጠን 26.8 ሺህ ኩንታል በብር 174.5 ሚሊዮን ሲሆን በዚህ ወቅት 16.4 ሺህ ኩንታል በብር 181.9 ሚሊዮን በመሸጥ የዕቅዱን በመጠን 61 በመቶ በዋጋ ደግሞ 104 በመቶ ማከናወን ችሏል፡፡

 

ኮርፖሬሽኑ በነሐሴ ወር ላይ ለመሸጥ ያቀደው የፍጆታ ሸቀጦች መጠን 17.13 ሺህ ኩንታል በብር 164.7 ሚሊዮን ሲሆን በዚህ ወቅት 22.8 ሺህ ኩንታል በብር 169.9 ሚሊዮን በመሸጥ ዕቅዱን በመጠን 133 በመቶ በዋጋ ደግሞ 103 በመቶ አከናውኗል፡፡