photo_2022-11-04_15-15-58.jpg

 

ኮርፖሬሽኑ ከዋና መ/ቤት ጀምሮ በሁሉም ዘርፎችና የክልል ግብይት ማእከላት ለሚገኙ የሥራ ሃላፊዎች እና ሰራተኞች የ2014 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2015 በጀት ዓመት የእቅድ ትውውቅ የማጠቃለያ መድረክ በአዳማ ከተማ ከጥቅምት 19-20/ 2015 ዓ.ም አድርጓል፡፡ ከማጠቃለያ መድረኩ አስቀድሞ በአዲስ አበባ (በሁለት ዙር)፣ በአዳማ፣ በሃዋሳ፣ በድሬዳዋ፣ በደሴና በባህር ዳር ተመሳሳይ መድረኮች ተካሂደዋል፡፡

በማጠቃለያ መድረኩ ላይ የኮርፖሬሽኑ ሥራ አስፈጻሚዎችና የዘርፎች ሥ/ አስፈጻሚዎች፣ ዳይሬክተሮች፣ የጽ/ ቤት ኃላፊዎችና የአራቱ ንግድ ስራ ዘርፎች በየደረጃው ያሉ የሥራ ሃላፊዎች እስከ ከፍተኛ ባለሙያ ተገኝተዋል፡፡ የውይይቱ ዋና ዓላማ በበጀት ዓመቱ ታቅደው የነበሩ ስራዎችን ክንውን በመገምገም የነበሩ ጥንካሬዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠልና የታዩ ችግሮችን ከምንጩ ለይቶ በ2015 በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

የ2014 በጀት ዓመት አፈጻጸምን አስመልክቶ በቀረበው ሪፖርት የመሠረታዊ ፍጆታ አቅርቦት /ግዥ/ የምርት ስርጭትና ተደራሽነት /ሽያጭ/ አፈፃፀም የአቅርቦት እጥረትንና የዋጋ ንረት ለመከላከል የተደረገ ጥረት በዝርዝር ቀርቦ አፈጻጸሙ ላይ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

የ2015 በጀት ዓመት እቅድን አስመልክቶ እቅዱ ሲዘጋጅ በየዘርፉ የቀረበውን ፍላጐት አቅምን ያገናዘበና ተልዕኮን ለማሳካት ቅድሚያ ትኩረት የሚሠጣቸውን በመለየት የተሰራ መሆኑን፣ ያለፉት በጀት ዓመታት ዕቅድ አፈፃፀም እንደ መነሻ በታሳቢነት የተወሰዱ መሆናቸው እና ዓለም አቀፋዊ እና ሀገራዊ የሁኔታ ትንተናዎች ግምት ውስጥ መግባታቸው በቀረበው ገለጻ ተመላክቷል፡፡ እቅዱ በዋነኛነት የገበያ ማረጋጋት ሥራን እና የገበያ ድርሻን በማሳደግ ዋናውን የኮርፖሬሽኑን ተልዕኮ ለማሳካት የሚያስችል እንዲሆን ታስቦ መዘጋጀቱ በገለጻው ተጠቅሷል፡፡

ኮርፖሬሽኑ እቅዱ ከያዛቸው ዋና ዋና ግቦች መካከል የግዢ ዕቅድን ስንመለከት በ2015 በጀት ዓመት ከተለያዩ የግዢ ምንጮች 3,102,318 ኩንታል ምርት በብር 11,104,108,556 ለመግዛት ዕቅድ የተያዘ ሲሆን የሽያጭ ዕቅድን በተመለከተ ደግሞ ኮርፖሬሽኑ በ2015 በጀት ዓመት የማረጋጋቱን ሥራ ጨምሮ በአገር ውስጥ እና በወጪ ግብይት ብር 12,674,763,285 ዋጋ ያለው ምርትና አገልግሎት ለመሽጥ ዕቅድ ይዟል፡፡ ከዚህ ውስጥ የሀገር ውስጥ ሽያጭ 12,069,480,785 ብር እና ኤክስፖርት ሽያጭ 605,282,500 ብር ይይዛሉ፡፡

የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቻ ደምሴ በማጠቃለያ መድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልእክት በ2015 በጀት ዓመት እቅድ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት ሁሉንም አቅም በመጠቀም የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ልዩ ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባል ብለው ከጠቀሷቸው ተግባራት መካከል የግዢ አፈጻጸም ትስስር፣ የደንበኞች አያያዝ፣ ኃላፊነትን በአግባቡ መወጣት እንዲሁም የሥራ አፈጻጸም አሞላልና ነጥብ አሰጣጥ የሚሉት ይገኙበታል፡፡

ኦፕሬሽናል ልቀት፣ የመፈፀም እና ማስፈፀም አቅም፣ የማያቋርጥ ለውጥና ተወዳዳሪነት እንዲሁም ስትራቴጂያዊ አጋርነት የኮርፖሬሽኑ የትኩረት መስኮች እንደሆኑ ተገልጿል፡፡

Acha_Message_New_Year.jpg

Evaluation.jpg

 

የኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን የበጀት ዓመቱ እቅድ አፈጻጸም ግምገማ ከነሐሴ 2-4/ 2014 ዓ.ም የኮርፖሬሽኑ ሥራ አስፈጻሚዎች፣ የዘርፎች ሥ/ አስፈጻሚዎችና እስከ ቡድን መሪ ያሉ የሥራ ሃላፊዎች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡ ለሶስት ቀናት የተካሄደው መድረክ ዓላማ፣ በበጀት ዓመቱ ታቅደው የነበሩ ስራዎች ክንውን በመገምገም የነበሩ ጥንካሬዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠልና የታዩ ችግሮችን ከምንጩ ለይቶ መፍትሄ በማስቀመጥ በ2015 በጀት ዓመት ውጤታማ ስራ ለመስራት ነው፡፡

በውይይቱ ለህብረተሰቡ በገበያ ማረጋጊያነት የሚቀርቡ መሰረታዊ የምግብ እህል ምርቶች፣ የፍጆታ ሸቀጦች፣ አትክልትና ፍራፍሬ አቅርቦት፣ ስርጭትና ተደራሽነት እቅድ አፈፃፀሙ ከደንበኞች ፍላጎት አንጻር መሆኑን የፋይናንስ ስራው በሲስተም በሚፈለገው ደረጃ IFRS ሂሳብ የመዝጋት አመታዊ የፋይናንስ ሪፖርትን በተሰጠ ግዜ ገደብ የማውጣት ሂደት ተከትሎ መሰራቱን እንዲሁም የሰው ሃብት ለማብቃት እና ሀብት አጠቃቀምን አሳድጎ ያለ ስራ የተቀመጡ ንብረቶችን አንቀሳቅሶ ውጤታማ ለማድረግ የተሰሩ ሥራዎች አፈፃፀም ላይ ትኩረት አድርጓል፡፡

የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አቻ ደምሴ ግምገማውን ሲያጠቃልሉ በአጠቃላይ በኮርፖሬሽን ደረጃ በዘርፎች፣ በዳይሬክቶሬቶች እና ጽ/ቤቶች በእቅድ አፈጻጸሞች ላይ የተደረገው ውይይት በባለቤትነት መንፈስ እና የኮርፖሬሽኑን ተልእኮ ለማሳካት እና ለህብረተሰቡ የምንሰጠውን አገልግሎት የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ መካሄዱን ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም በበጀት ዓመቱ በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቁመው፣ ያልተሰሩ ስራዎች በድክመታችን አለመከናወናቸውን ተቀብለን ሁሉንም ችግር በአንዴ መፍታት ባይቻል ቅድሚያ ለሚሰጠው ጉዳይ ቅድሚያ እየሰጠን እንሰራለን ብለዋል ፡፡

cement-1771678.jpg

መንግስት ከሲሚንቶ ምርት ግብይት አኳያ የሚታየውን ችግርና የዋጋ ንረት ለማረጋጋትና የምርት ስርጭቱን ቅደም ተከተል በማስቀመጥ ግብይቱን ግልጽና ተደራሽ ለማድረግ እንዲያስችል የአሰራር ስርዓት ዘርግቷል፡፡ በመሆኑም ከአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ በተላከው የሲሚንቶ ምርት፣ ግብይትና ስርጭት መመሪያ መሰረት የኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን ለሲሚንቶ ምርት ፈላጊዎች ሽያጭ እያከናወነ ይገኛል፡፡

አስፈላጊውን መረጃ ላሟሉ ለመንግስት ግንባታ እና ለግል ገንቢዎች እንዲሁም ለብሎኬት አምራቾች ከነሐሴ 17/ 2014 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሆነ የሽያጭ ፕሮግራም ኮርፖሬሽኑ ያወጣ ሲሆን ተጠቃሚ የሚሆኑት ክፍለ ከተሞች ቂርቆስ፣ ልደታ፣ አዲስ ከተማ፣ ኮልፌ ቀራንዮ፣ ጉለሌ እና ንፋስ ስልክ ላፍቶ ናቸው፡፡ ከነሐሴ 17- 27/2014 ዓ.ም የቂርቆስ፣ የልደታ እና የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተሞች ተጠቃሚ የነበሩ ሲሆን ከነሐሴ 28/ 2014 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ተጠቃሚ በመሆን ላይ ይገኛል፡፡ የጉለሌ እና ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተሞች ደግሞ በመቀጠል በወጣላቸው ፕሮግራም መሰረት ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡

 

 

001_6.jpg

የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን አመራርና ሠራተኞች በአራተኛውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር “የገበያ ማረጋጊያ ሥራችንን እያጠናከርን አረንጓዴ አሻራችንን እናሣርፋለን” በሚል መሪ ቃል ሆለታ በሚገኘው የኮርፖሬሽኑ የግብይት ማዕከል የችግኝ ተከላ አካሂደዋል፡፡ ከተለያዩ የኮርፖሬሽኑ የንግድ ሥራ ዘርፎች የተውጣጡ ሠራተኞችና የሥራ ሃላፊዎች በተገኙበት ቅዳሜ ሀምሌ 23 ቀን 2014 ዓ/ም በተካሄደው መርኃ ግብር ላይ ከ1,300 በላይ የቅመማ ቅመም፣ የፍራፍሬ፣ የግቢ ውበትና የጥላ ዛፎች ተከላ የተካሄደ ሲሆን በተመሳሳይ መርኃ ግብሮችም በኮርፖሬሽኑ የተለያዩ ቅርንጫፍ ማዕከላት መሰል የተከላ መርሃ ግብሮች ተከናውነዋል፡፡

 

የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቻ ደምሴ በችግኝ ተከላ መርኃ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት ኮርፖሬሽኑ በተለይም ካለፉት አራት በተካሄዱት አረንጓዴ ዐሻራ የማኖር አገራዊ ጥሪዎች የችግኝ ተከላና እንክብካቤ ክንውኖችን በስፋትና በተከታታይነት ሲያካሂድ መቆቱን አስታውሰው፤ እስካሁን በተካሄዱ የተከላ መርኃ ግብሮች ከተተሉት ችግኞች 84 በመቶው መጽደቃቸውን ገልጸዋል፡፡ በያዝነው ዓመትም ኮርፖሬሽኑ የተለያዩ የቅመማ ቅመም፣ የፍራፍሬ፣ የውበትና የጥላ ዛፎችን በሆለታ የግብይት ማዕከልና በሌሎችም የኮርፖሬሽኑ ቅርጫፍ ማዕከላት በማካሄድ ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡

 

የችግኝ ተከላ መርኃ ግብሩ በአካባቢ ጥበቃ ረገድ የደን ሽፋንን ለማሳደግ ብሎም አረንጓዴ ልማትን ለማረጋገጥ ከሚኖረው አስተዋጽዖ በተጨማሪ መልሰው ምርት መስጠት የሚችሉ ችግኞች የሚለሙበት በመሆኑ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

 

የአረንጓዴ ልማት እንዲሳካ እንደ አገር ሰፊ ርብርብር እየተደረገ መሆኑን ያወሱት ዋና ሰራ አስፈጻሚው፤ በተለይም ዓለም አቀፍ ደረጃ በስፋት እየተስተዋሉ የሚገኙ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎችን ለመቋቋም፣ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግና አፈር ለምነት እጦትን ለመከላከል የችግኝ ተከላ መርኃ ግብሩ ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ከመሆኑ አኳያ ሁሉም በየአካባቢው ሥራውን በተገቢው መልኩ ለመከወን የሚያስችል በቂ ዝግጅት፣ ትግበራና ክትትል በማድረግ የበኩሉን የልማት አስተዋጽዖ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡