በኮርፖሬሽን ደረጃ ወጥነት ያለው የመረጃ አደረጃጀትና ሥርጭትን በመጠቀም ለደንበኞች የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት የውስጥ መረጃ ልውውጦችንም ቀልጣፋና የተሟላ ለማድረግ በሚቻልበት አሠራር ላይ ያተኮረ ሥልጠና ነሀሴ 18 ቀን 2012 ዓ/ም በኮርፖሬሽኑ የስብሰባ አዳራሽ ተካሂዷል፡፡

በኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቻ ደምሴ በተሰጠው ሥልጠና የኮርፖሬሽኑ ም/ዋና የሥራ አስፈጻሚዎች፣ የዘርፍ ሥራ አስፈጻሚዎች፣ ከፍተኛና መካከለኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ የጽሕፈት ሥራና የቢሮ ውበት አስተዳደር ባለሙያዎች እንዲሁም የሪከርድና ማህደር ባለሙያዎች ተሣትፈዋል፡፡

ዓላማው የመረጃ አያያዝና አሰረጫጨትን በካይዘን ፍልስፍና በመታገዝ መረጃዎችን በቀላሉ ማግኘት ፣በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂን በመታገዝ የደብዳቤዎች ምልልስን በማስቀረት ግዜን እና ጉልበትን ከብክነት ማዳን የሚያስችሉ አሰራሮችን ማመላከት በሆነው ስልጠና መነሻነት የተለያዩ ውይይቶች ተደርገዋል፡፡

በሥልጠናው ማጠቃለያ በኮርፖሬሽን ደረጃ ወጥ የሆነ መረጃ አደረጃጀት እንዲኖር በሙያው የሚመለከታቸውን ባለሙያዎች ያቀፈ የመመሪያ ዝግጅት ኮሚቴ እንዲዋቀር ቀደም ብሎ ለመረጃ አያያዝ በግብዓትነት የተጠየቁ በተቻለ አቅም ግዥ እየተፈጸም እንዲቀርብ በሚመለከታቸው አካላት ትኩረት እንዲሰጥ ከስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡

የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ2013 ዕቅድ አፈጻጸምና በ2013 የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ከሁሉም የንግድ ዘርፎችና ከኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት ሠራተኞች ጋር አጠቃላይ ውይይቶች አካሂዷል፡፡ ውይይቶቹ በኢንሥኮ የበላይ አመራሮች ሰብሳቢነት የተካሄደ ሲሆን የተሳታፊዎቸን ለኮቪድ-19 ተጋላጭነት ለመቀነስ በሚያስችል መልኩ በዙር ጎተራ በሚገኘው ኮርፖሬሽኑ የስብሰባ አዳራሽ ነሀሴ 21፣ 22፣ 25፣ 26 እና 28 ቀን 2012 ዓ/ም ተካሂደዋል፡፡

የኢንሥኮን የ2012 ዓ/ም የንግድ ሥራዎች የሥራ አፈጻጸም በተመለከተ በቀረበው ሪፖርት ላይ ሽፋን ከተሰጣቸው ጉዳዮች መካከል የተቋሙ የ2012 ዓ/ም የግዢና አፈፃፀም የሽያጭ አፈፃፀም፣ ገበያን ከማረጋጋት አንፃር የተከናወኑ ዓበይት ተግባራት የሚገኙበት ሲሆን የሰው ሀብት ሥራ አመራርና ልማት፣ የፋይናንስ ሀብት አጠቃቀም፣ የኦዲትና ኢንስፔክሽን፣ የሪፎርምና የመልካም አስተዳደርና ሌሎችም ተቋማዊ ዕቅዶች አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

የግዢ ዕቅድ አፈጻጸምን በተመለከተ ኮርፖሬሽኑ በበጀት ዓመቱ 10.3 ሚሊዮን ኩንታል እህል፣ ቡና፣ የፍጆታ ዕቃዎች እና አትክልትና ፍራፍሬ በብር 11.3 ቢሊዮን ለመግዛት አቅዶ 7.9 ሚሊዮን ኩንታል በብር 8.7 ቢሊዮን በመግዛት የዕቅዱን በመጠንም ሆነ በዋጋ 77 በመቶ ማከናወኑ ተገልጿል፡፡

የሽያጭ አፈፃፀምን በተመለከተ ኮርፖሬሽኑ በ2012 በጀት ዓመት በሀገር ውስጥና በውጪ ገበያ ብር 8.9 ቢሊዮን ዋጋ ያለው 10.1 ሚሊዮን ኩንታል እህል፣ ቡና፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ የፍጆታ ዕቃዎች እንዲሁም የግዢና ማማከር አገልግሎት ለመሸጥ አቅዶ ብር 5.9 ቢሊዮን ዋጋ ያለው 7.0 ሚሊዮን ኩንታል ምርትና አገልግሎት በመሸጥ ዕቅዱን በመጠን 70 በመቶ በዋጋ ደግሞ 67 በመቶ ማከናወኑ ተጠቅሷል፡፡

ኮርፖሬሽኑ ሲሚንቶ ለተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያሰራጭ በመንግሥት በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ከፋብሪካዎች በመረከብ በሥርጭት እንዲሸፍናቸው በተሰጡት አካባቢዎች የ25.8 ብር ሚሊዮን ዋጋ ያለው 83.6 ሺህ ኩንታል ሲሚንቶ ጠቅላላ ሽያጭ አከናውኗል፡፡

በግዢና ሽያጭ አፈጻጸም ላይ ተጽዕኖ ካሳደሩ ምክንያቶች መካከል የመግዣ ካፒታል እጥረት፤ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ምርትን የማስተዋወቅና ገበያ የማፈላለግ ሥራ በበቂ ሁኔታ አለመሠራቱ፣ እሴት ጨምሮ መሸጥ ላይ ትኩረት አለመደረጉ፤ የውጭ ደንበኞች የሚሠጡት ዋጋ በተለይም የቡና፣ ቅባት እህልና ጥራጥሬ ዋጋ ወጪን ሸፍኖ ለመሸጥ የማያስችል ዝቅተኛ ዋጋ መሆን፤ የግል ላኪዎች በኤክስፖርት የሚደርስባቸው ኪሣራ በሚያስገቡት ሸቀጥ ስለሚያካክሱት ዋጋ ሰብረው መሸጣቸውና በሚፈለገው መጠን ለሽያጭ መደብሮች የሸቀጥ አቅርቦት ማቅረብ አለመቻሉ፤ ከባንክ ኦቨር ድራፍት /ብድር/ በመግባት እንዲፈታ እየተደረገ ቢሆንም ብድሩ ከፍተኛ የወለድ ወጭ ያለው መሆኑ፣ የሀገር ውስጥ ስንዴ መግዣ ዋጋ በእጅጉ መጨመር፤ በኮሮና ፋይረስ ወረርሽን ምክንያት የእህል አቅርቦት መቀነስና የዋጋ መጨመር፤ የሚሉት ውስጣዊና ውጫዊ ተግዳሮቶች ይገኙበታል፡፡

የአመራሩን ሁኔታ በተመለከተም አመራሩ የተሰጠውን ተግባር በቅንነት ተቀብሎ ለመፈፀም ጥረት የሚያደርግ መሆኑ፤ የነበረውን የአመራር ክፍተት ሸፍኖ በመስራት በኩል የነበረው እንቅስቃሴ በተለይ ከቅርብ ወራት ወዲህ የነበሩትን ችግሮች ለይቶ የተሸሻሉ አሰራሮቸን ሥራ ላይ በማዋል የተቀናጀ እንቅስቃሴ መደረጉ አንዲሁም ኮርፖሬሽኑን ትርፋማና ውጤታማ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት አበረታች መሆኑ በጥንካሬ የተመላከተ ሲሆን በየዘርፉ የተበተነ አሠራር መኖሩ፤ ተቋሙ እንደ ኮርፖሬሽን የተደራጀና የተጠቃለለ ሆኖ አለመመራቱ፤ ከቀመጡ የአሠራር መመሪያዎች ውጭ የሚፈፀሙ ተግባሮች መኖራቸው በድክመትነት ተገምግመዋል፡፡

በቀጣይ እንደ ተቋም አፈጻጸምን ለማሳደግ በትኩረት አቅጣጫነት ከተቀመጡ ጉዳዮች መካከልም አፈጻጸሞች አጠናክሮ ማስቀጠል፣ ጉድለትና ድክመት የታየባቸውን በማሻሻል ወደተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር አልሞ መስራት፣ ውጤታማ የሀብትና ንብረት አጠቃቀምን ተግባራዊ ማድረግ፣ የተለያዩ የገበያ መረጃዎችን በጥራትና በስፋት ከአምራቹ፣ ከአቅራቢው፣ ከተጠቃሚው በማሰባበስብ ሥራ ላይ ማዋል፤ በወጪ ንግድ ያላሰለሰ ጥረትና ድጋፍ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ማሣደግ እንዲሁም ልዩ ልዩ አጋዥ ሪፎርሞችን ሥራ ላይ ማዋልና የደንበኞችንና ባለድርሻ አካላትና ተጠቃሚዎችን እርካታ ማሣደግ ትኩረት ሊሰጣቸው እንደሚገባ የጋራ ግንዛቤ ተወስዷል፡፡

Harbour

 

በዓለም አቀፍም ሆነ በአገራዊ የንግድ እንቅሰቃሴ ውስጥ በተለይም ምጣኔ ኃብትን የሚያንቀሳቅሱና የንግድ ሥርዓቱ አካላትና ማኅበረሰቡ ተሣታፊ በሆኑበት የንግድ ሥራ ውስጥ የተደራጀና ሥራዎችን በቀላጠፈ አኳኋን ለማስኬድ የሚያስቸል የሎጂስቲክስ አገልግሎት ለአገልግሎት ሰጪው የጀርባ አጥንት ነው፡፡ በዚህ ረገድ ኢንሥኮ የሚያካሄዳቸው ምርት ተኮር የሆኑ የንግድ እንቅስቃሴዎች በምርት በአገር አቀፍ ደረጃ በሚከናወኑ የምርቶች ግብይትና ዝውውር ላይ የተመረከዙ እንደመሆናቸው ለዚሁ አገልግሎት የሚውሉ ተሸከርካሪዎች መኖርና በአግባቡ ሥራ ላይ መዋል መሠረታዊ ነው፡፡ አገልግሎቱ የምርት ግዢና ሽያጭ ሥራዎችን በማቀላጠፍ ተገቢውን አገልግሎት በተገቢው ጊዜ እንዲሠጥ ያስችላል፡፡

 

ለዚሁ አገልግሎት መሳለጥም ለተሸከርካሪዎች መደበኛና የተሟላ ጥገና ማድረግ የሚያስችል የመሣሪያና የጥገና ማዕከል ያስፈልጋል፡፡ በኮርፖሬሽኑ የእህልና ቡና ማደራጃ ማዕከል የሚገኘው የሎጂስቲክስ አገልግሎት የሥራ ክፍል ይህን አገለግሎት ለበርካታ ዓመታት ሲሰጥ ቆይቷል፤ እየሰጠም ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ የአገልግሎት አንድ አካል የሆነው የተሸከርካሪዎች ጥገናና እንክብካቤ አገልግሎቶች ሲሰጡባቸው የነበሩ አውታሮች ከኮርፖሬሽኑ የንግድ ሥራዎች ስፋትና አቅም ተመጣጣኝ ሳይሆኑ በመቆየታቸው ለባለሙያዎችና የሥራ አፈጻጸም ማነቆ ሆኖ ቆይቷል፡፡ በተለይም ጥገናዎች የሚናወኑበት ደረጃውን የጥገና ማዕከል ባለመኖሩ የቴክኒክ ባለሙያዎች ጸሐይና ዝናብ እየተፈራረቀባቸው መሣሪዎችም ለብልሽት ተጋላጭ ሆነው አገልግሎቱ ሲሰጥ ቆይቷል፡፡

 

ይህን ማነቆ ለመፍታትና የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል ኮርፖሬሽኑ በቅርቡ በወሰደው እርምጃ ለባለሙያዎችና ለተቀላጠፈ አሠራር በሚያመች መልኩ የአዳዲስና ዘመናዊ ጥና ማዕከሎች ግንባታ ተጀምሮ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፡፡ ግንባታው በአንድ ጊዜ ለ17 ተሸከርካሪዎች አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ሲሆን ባለሙያዎችም በማንኘውም የአየር ሁኔታ ሥራቸውን ማከናወን የሚችሉበት ነው፡፡

COVID 19 Fight

 

በቅርብ ጊዜ ውስጥ የተከሰተውና በፈጣን ሁኔታ በሁሉም አህጉራት እተሰራጨ የሚገኘው የኮሮናቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽን ወደ ኢትዮጵያ ከገባ ጀምሮ መንግሥት የቫይረሱን ስርጭት በመከላከል ከፍተኛ እንቅሳቀሴ እያደረገ ይገኛል፡፡ ይህንንም ተግባራዊ ከማድረግ አኳያ የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሠራተኛውን ደህንነት በመጠበቅ ለህብረተሰቡ የሚሰጠው አግልጎሎት ሳይቋረጥ ለመቀጠል እንዲቻል የድርጊት መርሃ ግብር አዘጋጅቶ የተለያዩ እንስቃሴዎች ማናወን ከጀመረ ሰነባብቷል፡፡ የበሽታው ስርጭት በሠራተኛ ጤንነት፣ በኮርፖሬሽኑ ግብይት እና ገቢ ላይ ተፅዕኖ በመተንበይና ይህንንም ተፅዕኖ የሚያሳድር ከመሆኑ አኳያ የድርጊት መርኃ ግብሩ በእነዚህ ላይ ትንተና በማካሄድ ችግሩን መቋቋም የሚቻልበት አሠራር ነድፎ ወደ ትግበራ ጀምሯል፡፡

 

የኮቪድ-19 ሥርጭትን የመከላከሉ መርኃ ግብር በሽታው በኮርፖሬሽኑ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ላይ የሚያደርሰውን ተጽዕኖ ትንታኔ መነሻ ያደረገ ነው፡፡ ሠራተኞች ከሥራቸው ባህሪ አንጻር በተለይም ከደንበኞች መስተንግዶ ጋር በተያያዘ ተጋላጭ መሆናቸው፤ ሠራተኞች በጋራ የሚጠቀሙባቸው የመገልገያ መሣሪያዎች መኖራቸው፤ ሠራተኞች በተበታተነና በተለያዩ ቦታዎች የሚኖሩ መሆኑ የተጋላጭነት ስጋትን የሚጨምር መሆኑ እንዲሁም ከአጠቃላይ ከቫይረሱ ስርጭት መስፋፋት ጋር በተያያዘ ሠራተኛው ለበሽታው እጋለጣለሁ በሚል የስነ ልቦና ጫና የሚያድርበት መሆኑ ለመከላከል ሥራዎች መነሻ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው፡፡

 

የኮርፖሬሽኑን ዓበይት የንግድ ተግባራት ጋር በተያያዘም ከታዳጊ አገሮች ከፍትኛ ምርት የሚያስገቡ እንደ ቻይና፣ አውሮፓና አሜሪካና ሌሎችም ያሉ አገራትና አህጉራት የንግድ እንስቃሴቸው በመገደቡ የተነሳ ከውጭ የሚያስገቡት ምርት ፍላጎት አብሮ በመቀዝቀዙ ኢትዮጵያ ጨምሮ ሌሎች ታዳጊ አገራት ወደ ውጭ ይልኩት የነበረው ምርት በመጠንም ሆነ በዋጋ መቀነሱ በችግርነት ተጠቅሷል፡፡ የበሽታው ሥርጭት በአጭር ጊዜ የቀንሳል ተብሎ ስለማይጠበቅ ኮርፖሬሽኑ የገጠመውን ኤክስፖርት መቀዛቀዝ እሰከ ሚቀጥለው በጀት ዓመት አጋማሽ እንደሚቀጥል መገመቱ በስጋትነት ተቀምጧል፡፡

 

የቫይረሱን ወረረርሽ ለመከላል በሚሰጠው ቅድሚያ ትኩረትና በሌሎች ምክንያቶች የውጭ ምንዛሪ ዕጥረቱ ችግር ባለመቀረፉ በኮርፖሬሽኑ የውጭ ምርቶችን በማስገባት ሂደት ላይ ተትዕኖው ሊበረታ እንደሚችል የገመተ ከሞኑ ባሻገር የኤክስፖርት ገበያ መቀዛቀዝ እና በሀገር ውስጥ የእርዳታ ድርጅቶች (እንደ ዓለም ምግብ ፐሮግራም እና አደጋ ስጋትና ዝግጁነት ኮሚሽን ዓይነት) የእህል ዋጋ በመጨመሩ የተነሳ በሀገር ውስጥ የሚገዙት የነበረ መጠን መቀንስ የተነሳ የኮርፖሬሽኑ እህል ሽያጭ በተለይም ከፍተኛ ድርሻ ያለው በቆሎ ሽያጭ ቀንሶ መታየቱና ይህም በተራው የኮርፖሬሽኑ የትርፍ መጠን ይቀንሰቀዋል ተብሎ መጠበቁ በንግድ ሥራ ተጽዕኖነት ተቀምጠዋል፡፡

 

እነዚህን ችግሮች ለመፍተታት ኮርፖሬሽኑ የተለያዩ የበሽታውን ሥርጭት የመቋቋሚያ ትግበራዎች ነድፎ ተንቀሳቅሷል፡፡ በዚህም በተዋርድ ኮሚቴ በማቋቋም ስለወረርሽኙና የመከለከያ ዘዴው ሠራተኛው የተሟላ ግንዛቤ እንዲኖረው የተለያዩ የተግባቦት ሥራዎች የተከናወኑ ሲሆን በሥራ ገበታ የሚኖረው ሠራተኛ በተቻላ ቦታ ለመቀነስ እንዲቻል የተጠራቀመ የአመት ፈቃድ ያላቸው ሠራተኞች ፈቃዳቸውን እንዲወስዱ ወይም በቤታቸው ሆነው እንዲሠሩ ማድረግ ተችሏል፡፡ የጤና ችግር ያለባቸው ሠራተኞች በተቻለ መጠን ዕረፍት እንዲወስዱ ማድረግ፣ በቅብብሎሽና በቅርርብ የሚሰሩ ሥራዎች አካባቢ ሠራተኞች ርቀታቸውን እንዲጠብቁና በቂ የአየር ዝውውር እንዲኖር ማድረግ፤ የጋራ መጠቀሚያ መሳሪያዎችን ፅዳታቸውን የጠበቁ እንዲሆን ማድረግ፤ ሠራተኞች ወደ ስራ ሲገቡ እና ወደ ክሊኒክ ለህክምና ሲሄዱ በሙቀት መለኪያ መሳሪያ ሙቀታቸውን እንዲለኩ ማድረግ እንዲሁም የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማስክ ሠራተኞች እንዲጠቀሙ በማድረግ በሽታውን የመከላከል ጥረቶች ተደርገዋል፡፡

 

በአዲስ አበባ ውስጥ ያሉ የኮርፖሬሽኑ ይዞታዎች የበለጠ ለቫይረሱ ተጋላጭ ናቸው የተባሉ የሥራ ቦታዎች ተለይተው ሥራ አመራሩን ያካተተ ተደረጎ በግብረመልስ ላይ የተመሠረቱ ርምጃዎች ተወስደዋል፡፡ የሰራኞች ሰርቪስ እጥረትን ለመፍታት ከሎጂስቲክ ጋር በመመካከር ተጨማሪ መኪኖች እንዲመደቡ ተደርጓል፡፡ የንጽህና መጠበቂያ ሰኒታይዘሮችን፣ አልኮልና ፈሳሽ ሳሙና ለሰራተኞች እንዲከፋፈል የተደረገና ሲሆን ከእጅ ንክኪ ነጻ በሆኑ የእጅ መታጠቢያዎች እንዲጠቀሙም ተደርጓል፡፡

 

ከግብይት ሥራዎች ጋር ተያይዞ በኤክስፖርት ገበያ እየገጠመ ያለውን የገበያ መቀዛቀዝ ለመቋቋም በዝቅተኛ ትርፍ ወይንም ወጪን ብቻ በሚሸፍን መልኩ ዋጋ በመስጠት ለማበረታታት ጥረት በማድረግ፣ ከከፍተኛ ምርት አምራቾች ወይም ኢንቨስተሮች ጋር ተቀራርቦ በመሥራት ምርታቸው ለኮርፖሬሽኑ የሚያቀርቡበት መንገድ በቀጥታ በመደራደር እንዲሁም በውጭ ምንዛሪ እጥረት እየገጠመ ያለውን መሠረታዊ ሸቀጥ በበቂ ሁኔታ ለህብረተሰቡ ያለማቅረብ ችግር ለመቅረፍ ኮርፖሬሽኑ ከኤክስፖርት የሚያገኘውን ገቢ በተቻለ መጠን ከውጭ ሸቀጥ የሚያስገባበትን ሁኔታ ከባንኮች እና ሌሎች የሚመለከታቸው ጋር በመነጋገር ችግሩን ለመቋቋም እየተሠራ ይገኛል፡፡

 

በተጨማሪም ኮርፖሬሽኑ ሊደርሰው የሚችለው የንግድ ኪሣራ ለመቋቋም በተቻለ መጠን ሌሎች የገቢ ማስገኛ ስልቶች ላይ ጠንክሮ መሥራት እንደሚኖርበትና የበቆሎ እና ሌሎች እህሎች ሽያጭ እንደተጠበቀው ባለመሆኑ በአሁኑ ወቅት ፍላጎታቸውን እየጨመረ የመጣውን የኢንዱስትሪ ሸቀጦችና እንደዚሁም አትክልትና ፍራፍሬ ሽያጭ ላይ በርትቶ በመሥራት የሽያጭ ሥራዎችን አጎልብቶ መንቀሳቀስ እንደሚያስፈልግ በተቋም ደረጃ የጋራ ግናዛቤ የተወሰደበት ጉዳይ ሆኗል፡፡

Consumer products 2

 

የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በፍጆታ ሸቀጦች ንግድ መስክ በአገሪቱ የንግድ ሥርዓት ውስጥ የሚስተዋሉ የተዛቡ የንግድ አሠራሮችን ለማስተካከል፣ ለዋጋ ግሽበት መንስዔ የሆኑ አሠራሮችን ለመፍታት፣ የተለያዩና በርካታ ሸቀጦችን በአንድ ሥፍራ ተደራሽ ለማድረግ እንዲሁም በንግድ ሥርዓቱ ውስጥ ዘመናዊ የንግድ አሠራርን ለማስፈን እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ ኮርፖሬሽኑ ቀደም ሲል “አለ በጅምላ” መጠሪያ ይታወቅ የነበረው የንግድ ዘርፍ ሲመሠረት የተፈጠሩና የፋይናንስ ማነቆዎችንና ውጣ ውረዶቸን በመቋቋም ተልዕኮዎቹን በተለይም የገበያ ላይ ውድድርን በብቃት አሸንፎ ገበያን ከማረጋጋትና የህብረተሰቡን የመሠረታዊ ሸቀጦቸ ፍላጎት ከማሟላት እንዲሁም ለአገር ውስጥ አምራቾች የገበያ ዕድልን ከመፍጠር አኳያ እየሠራ ይገኛል፡፡

 

ኮርፖሬሽኑ በዚህ ዘርፍ ስላከናወናቸው ዓበይት ተግባራትና አገራዊ እንዲሁም በዓለመ አቀፍ ደረጃ በሁሉም ማኅበረ-ኤኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ላይ የሚገኘው የኮቪድ-19 በሽታ በግብይት ሥራ ላይ ስላስከተለው ተጽዕኖ፣ አንዲሁም በሸማቹ ኅብረተሰብ በተለይም ዝቅተኛ የኤኮኖሚ አቅም ያላቸው ላይ የተፈጠረውንና ለወደፊትም ሊፈጠር የሚችለውን የሚፈጠረውን ኤኮኖሚያዊ ጫና ከመቋቋም አኳያ ዘርፉ በምርት ክምችትና እና አቅርቦት ረገድ እያከናወ ያለውን ሥራ በዚህ ጽሑፍ እንዳስሳለን፡፡

 

የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን አንድ የንግድ ዘርፍ የሆነው የፍጆታ ዕቃዎች ንግድ ሥራ ዘርፍ በአለ በጅምላ ሥያሜ ሲቋቋም ምርቶችን 60 በመቶ ከውጭ በማስገባትና እና 40 በመቶውን ከአገር ውስጥ አምራቾች በመግዛት ነበር የአገሪቱን ገበያ የማረጋጋት ሥራን ሲከናውን ቆቷል፡፡ ዘርፉ በአሁኑ ወቅት የአገር ውስጥ ኩባንያዎችን ለማበርታትና የውጭ ምንዛሬንም ለማዳን ከውጭ የሚያስገባውን ምርት መጠን በመቀነስ አብዛኛውን ምርት ከአገር ውስጥ በመግዛት ለገበያ ያቀርባል፡፡ በዚህም ከበርካታ ኩባንያዎች ጋር የገበያ ትስስርን መፈጠር ችሏል፡፡ የንግድ ዘርፉ ለሽያጭ የሚያቀርባቸው ምርቶች (ለስላሳ መጠጦች፣ የፍጆታ ሸቀጦች ፣ የታሸጉ ምግቦች፣ የቤትና የግል ንጽሕና መጠበቂያዎች፣ የጽሕፈት መሣሪያዎች፣ የምግብ ዘይትና ስኳር ምርቶችን በመንግሥት በሚወጣ የዋጋ ተመን መሠረት እንደ መሣሪያ በመሆን ለኅብረተሰቡ ያደርሳል፡፡ የምርቶችን ሚዛናዊ ሥርጭት ለመረጋገጥም አካባቢው የሚገኙ የንግድ ቢሮዎች በሚያቀርቡት መረጃ መሠረት ምርቶችን በማሠራጨት የገበያ ማረጋጋት ሥራውን በከፍተኛ ደረጃ እያከናወነ ይገኛል፡፡

 

የንግድ ዘርፉ ለሸማቹ የሚያቀርባቸው አብዛኞቹ የለስላሳ መጠጦች፣ ዱቄት፣ የታሸጉ ምግቦች፣ የንጽሕና መጠበቂያዎች፣ መቆያና ጣፋጭ ምግቦች ሙሉ በሙሉ ለማለት ለሚያስችል ደረጃ ከአገር ውስጥ አምራቾች የሚቀርቡ ናቸው፡፡

 

በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተውና ተጽዐኖወ ከቀን ወደ ቀን እያየለ የመጣው የኮቪድ-19 በሽታ እንደማንኘውም የኤኮኖሚ ዘርፍና የንግድ ተቋም ሁሉ በኮርፖሬሽኑ የፍጆታ ዕቃዎች ንግድ ላይ ተጽዐኖ ማድረሱ አልቀረም፡፡ ከዘርፉ እንቅስቃሴ ጋር በተየያዘ በሽታው የሠራተኞችን ሙሉ አቅም ተጠቅሞ ሥራዎቹም ማከናወን የሚችልበትን አቅም መቀነሱና በተወሰነ ደራጃመ ቢሆን ስን-ልቦናዊ ጫና ማድረሱ አልቀረም፡፡ በተለይም የዘርፉ የንግድ ሥራ ከውጭ ምርቶችን በዋነኝነት የበሽታው ሥርጭት በተስፋፋበት በጅቡቲ በኩል የሚገቡ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በአሽከርካሪዎችና በሌሎችም ላይ ስጋት ወለድ ተጽዕኖ ፈጥሯል፡፡ ይሁን እንጂ ለእነዚህ ችግሮቸ ሳይበገር የተወሰኑ ሠራተኞች በፈረቃና ከቤት ሆነው መሥራት የሚችሉበትን ሁኔታ በማመቻቸት በዚህ ወቅት እንደ ወታደር ከፊት በመቆም ኅበረተሰቡ የምግብና ሌሎች የፍጆታ ዕቃዎችን ማግኘት እንዲችልና የተቸገሩ ሰዎችም የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ በተለይ በዱቄት፣ በፓልም ዘይት፣ በፓስታና ማካሮኒ አቅርቦት ረገድ ከወትሮው በተለየ የላቀ ሥራ በመሥራት ላይ ይገኛል፡፡

 

በበሽታው ምክንያት የኤኮኖሚ ተጽዕኖ ስር ለወደቁ ወገኖች በተለይም ለአረጋውያን ዕርዳታ የሚያደርጉ ድርጅቶች ከክፍለ ከተማ እና ከከተማ አስተዳደሩ ይዘው በሚመጡት መረጃ መሠረት የዱቄት፣ ፓስታ፣ ማካሮኒና ሌሎችንም ምርቶች ያለምንም ውጣ ውረድ ገዝተው እንዲያቀርቡ አስተዋጽዖ እያደረገ ይገኛል፡፡

 

የበሽታው የሥርጭት አድማስ እየሰፋ ከመሄድ አኳያ ወደፊት ሊፈጠር የሚችለውን የሸቀጥ እጥረት ከወዲሁ ለመከለከልም በተጨማሪም የንግድ ዘርፉ የሽያጭ ማዕካት በሚገኙባቸው በሁሉም አካባቢዎች ለሚገኙ አስከ 97 ሺህ የሚደርሱ የመንገሥት ሠራተኞች በወርኃዊነት የቀጥታ ግዢ እንዲፈጽሙ በማድረግ ተጽዕኖውን ለመቀነስ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል፡፡ ለአብነትም ከ46 ኮንቴይነር በላይ ፈሳሽ ዘይት ከውጭ በማሰመጣት እንዲሁም በቂ የዱቄት ምርት በመያዝ በሁሉም የሽያጭ መጋዘኖች በበቂ ሁናቴ እንዲኖር በማድረግ ሊከሰት የሚችለውን የዋጋ ንረት ለማረጋጋት የተቻለ ሲሆን ከተለያዩ ክልሎች የሚመጡ ተጠቃሚዎች የሽያጭ አገልግሎት እንዲያገኑ ተደርጓል፡፡

 

ለኮርፖሬሽኑ የሚቀርብ ምርትን በተመለከተ በተለይ ከውጭ የምርት ግብዓቶችን (ጥሬ ዕቃ) አስመጥተው የሚያመርቱ ኩባንያዎች ላይ ኮቪድ-19 ችግር መፍጠሩ አልቀረም፡፡ በዚህ ረገድ ኮርፖሬሽኑ የተለያዩ አማራጮችን በመውሰድ ምርት በቅድሚያ የሚያገኝበትን ዕድል በመፍጠር ከምንጊዜውም በተሻለ ሁኔታ ምርት በመጋዘን በመያዝ ለማኅበረተሰቡ ምርቶችን ተደራሽ በማድረስ ላይ ነው፡፡ በተለይም በአዲስ አበባ፣ በደሴና በሻሸመኔ ቅርንጫፎች በቂ ምርት እንዲኖር ተደርጓል፡፡

 

ሠላም ለሁሉም ማኅበራዊና ኤኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች መሠረት ነው፡፡ ሠላም በታጣ ቁጥር አምራችና የንግድ ተቋማት ሁሌም ስጋት ውስጥ መውደቃቸው አይቀርም፡፡ በቅርቡ የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በአገሪቱ በተከሰተው ሁከት ምክንያት በአዲስ አበባና ሻሸመኔ የሚገኙ የኮርፖሬሽኑ የፍጆታ ዕቃ መደብርና መጋዘኖች በመዘጋታቸው ለተወሰኑ ቀናት ለኅብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት ሳይቻል ቀርቷል፡፡ በሌላም በኩል የተስተጓገለውን የሽያጭ አገልግሎት የደሴ፣ የባህር ዳርና የአዋሳ የሽያጭ መደብሮች ተጨማሪ አቅም ፈጥረው እንዲሠሩ በማድረግ ለማካካስና ችግሩን ለመቋቋም ጥረት ተደርጓል፡፡

 

ኢንሥኮ በቀጣዮቹ 10 ዓመታት የንግድ ሥራውን አፈጻጸምና ፋይዳ ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ዕቅድ ነድፎ መንቀሳቀስ ከጀመረ ሰነበብቷል፡፡ በተለይም ለኦፕሬሽን ሥራዎች ልቀት ቀዳሚ ትኩረት በመስጠት በግዥና ሽያጩ እንቅስቃሴ ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ለአምራቹ ገበያ የመፍጠር ዕድል እና የሸማች ገበያን የማረጋጋት ሚና በአግባቡ ለመወጣት እየሠራ ይገኛል፡፡ በፍጆታ ሸቀጦች ግብይት እንቅስቃሴ ትኩረት ከተሰጣቸው ሥራዎች አንዱ የሽያጭ መደብሮችን ቁጥር ከፍ ማድረግ ነው፡፡ ለዚህም ከክልሎች ጋር ተቢውን ተግባቦት በማካሄድ በየዓመቱ ቢያንስ ሁለት ተጨማሪ የሽያጭ መጋዘንና መደብሮችን በመክፈት ለህብረተሰቡ በተሻለ ተደራሽ ለመሆን ታስቧል፡፡ በጅማ፣ አዳማ፣ መቀሌ፣ ጎንደርና ወልቂጤ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ ሥራዎች መጀመራቸውም ታውቋል፡፡

 

የአገር ውስጥ አምራቾች ጋር በተሻለ ቅርበት በመሥራትና የአገር ውስጥ ምርትን በማበረታታት የኅብረተሰቡን ፍላጎት ያገናዘበ አግልገሎት ለመስጠት የሚያስችሉ ተገባራት ም የስትራቴጂክ ዕወቅዱ አካላት ናቸው፡፡ ይህም ተጨማሪ የሥራ ዕድልን፣ አገልግሎትንና ትርፍን የሚያስገኝ በመሆኑ የኮርፖሬሽኑን አቅም የማጠናከር አቅም እንደሚኖረው ይታመናል፡፡

 

ከውጭና ከአገር ውስጥ አምራቾ ጋር የተጠናከረ ግንኙነት በማረግ በቂና አስተማማኝ የምርት አቅርቦት እንዲኖር የማድረግ፣ እንደ ዲመሬጅ ያሉ አላስፈላጊ ወጪዎችን መቀነስ እንዲሁም መጠነ ሰፊ ማዕካለዊ መጋዘን በማስገንባት በቂ ስቶክ ለመያዝና በጥቅሉ የገበያ ላይ ተወዳዳሪነትንና ትርፋማነትን ለማሳደግ ተወጥኗል፡፡

 

ኮርፖሬሽኑ በዚህ የንግድ ዘርፍ ቶሎ ቶሉ በሚሸጡ የፍጆታ ሸቀጦችን ግብይት ላይ የተሠማራ ከመሆኑ አኳያ ሁሉንም የኮርፖሬሽን ዘርፎች ይዞ መውጣት የሚችልበት እምቅ አቅም ያለው በመሆኑ ለዚህ ማነቆ የሆኑ በተለይም ከሂሳብ መዝጋትና ተገቢ ያልሆኑ ዕዳዎችን ከማሠረዝ ጋር የተያያዙ ችግሮችን ለመፍታት ከፍተኛ ጥረቶች በመካሄድ ላይ ይገኛሉ፡፡ ከስትራቴጂያዊ ሥራዎች በተጓዳኝም ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ  ለመደበኛ ሥራዎች ሰፊ ትኩረት በመስጠትና በጠነከረ አቅም በመሥራት ወደ ትርፋማነት ለመምጣት እየተሠራ የሚገኝ ሲሆን፤ የኮርፖሬሽኑ አዲስ አመራር ከዕዳ ክፍያ ጋር ለተያያዙ ማነቆዎች እልባትን በማስገኘት ጠንካራና ለሌሎች ተጓዳኝ የኮርፖሬሽኑ ሥራዎች ጭምር አቅምን ሊፈጠሩ የሚችሉ ሥራዎችን ለመከወን እየሠራ ይገኛል፡፡