Tree Planting 2012 EC s

በክረምት ወራት ችግኞችን በመትከል የተራቆተውን የአገራችንን የደን ይዞታ የመመለሱ ተግባር ላለፉት በርካታ ዓመታት በአገራችን ሲተገበር መቆየቱ አይዘነጋም፡፡ ይሁን እንጂ ከጊዜ ወደጊዜ እየሰፋ በመጣው ዓለም አቀፋዊ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖና የበርሃማነት መስፋፋት ምክንያት ትገበራው የተፈለገውን ውጤት ሳያመጣ ቆይቷል፡፡ ይህን ከግንዛቤ በማስገባት መንግሥት በተለይም ካለፈው ዓመት ጀምሮ አገራዊውን የችግኝ ተከላ ፕሮግራም በጎለበተና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ባተፈ መልኩ “የዜጎች የአረንጓዴ አሻራ ቀን እናሳርፍ፤ በአንድ ጀንበር 200 ሚሊየን ችግኝ እንትከል!” በሚል መርህ በአገር አቀፍ ደረጃ 4 ቢሊየን ችግኞች እንዲተከሉ ተደርጓል፡፡

 

የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽንም ሁሉንም ሠራተኞቹን በማስተባበር በድምሩ 12 ሺህ ያህል ችግኞች በመትከልና በመንከባከብ ለአገራዊ ግቡ መሣካት የራሱን አስተዋጽዖ ማድረጉና የታሪክ አሻራ ባለቤት መሆኑ አይዘነጋም፡፡ ዘንድሮም “5 ቢሊየን ዛፎች ለአረንጓዴ ኢትዮጵያ፡ አረንጓዴ አሻራችንን ማሳረፋችንን እንቀጥላለን” በሚል መርህ እየተካሄደ በሚገኘው የችግኝ ተከላ መርኃ ግብር አካልነት ሐምሌ 4 ቀን 2012 በሁሉም የኮርፖሬሽኑ ማዕከላት ቡድን በተደራጁ ሠራተኞቹ አማካኝነት የችግኝ ተከላ አካሂዷል፡፡

 

መርኃ ግብሩ የኮርፖሬሽኑ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በሎጂስቲክስና የቴክኒክ አገልግሎት ቅጥር ግቢ የተጀመረ ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ባሉ የኮርፖሬሽኑ ግቢዎች ማለትም በፍጆታ ዕቃዎች ንግድ ሥራ ዘርፍ ዋና  መ/ቤትና መገናኛ ቅርንጫፎች፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ንግድ ሥራ ወና መ/ቤት፣ በአቃቂ፣ በእህልና ቡና ንግድ ዘርፍ የቡና ማደረጃና ማከማቻ ማዕከል፣ በአደይ አበባ ግቢና በአዲስ አበባ ዙሪያ ግብይት ማዕከል ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ፣ አካባቢ ጥበቃ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጾ ያላቸውንና ለውበት የሚያገለግሉ 1500 ያህል ችግኞች ከ450 በላይ ሠራተኞችን በማሳተፍ ተከላው ተካሂዷል፡፡ በተጨማሪም ከአዲስ አበባ ውጪ በሚገኙ ቀሪዎቹ የኮርፖሬሽኑ ቅርንጫፍ መ/ቤቶች 10 ሺህ ችግኞችን የማስተከል ሥራዎች ከወዲሁ ተጀምረዋል፡፡

 

በቀዳሚው ዓመት የተከናወነው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በሠራተኛው ዘንድ ጥሩ መነሳሳትንና እንደ አገር ለአረንጓዴ ልማት ያለውን ጠቀሜታን በተመለከተ ግንዛቤን የፈጠረ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን፤ በዚህ ዓመትም ከችግኝ ተከላ በኋላ በሚዘጋጀው የችግኝ ተከላ ፕሮግራም የመንከባከብ ሥራ እንደሚከናወንና በዚህም የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ ዝግጁነት መኖሩን ተገልጧል፡፡

 

ለአትክልትና ፍራፍሬ ዛፎች ልዩ ትኩረት በተሰጠበት በዘንድሮው የተከላ ፕሮግራም ኮርፖሬሽኑ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ ብቻ 300 የአቮካዶ፣ 350 የማንጎ፣ 210 የዘይቱንና 220 የሎሚ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን 710 የጃካራንዳና 210 የሚሊያ ዛፍ ችግኞች ተከላም ተከናውኗል፡፡ የእንክብካቤ ሥራዎችም ለአፈጻጸም በሚያመች መልኩ ሠራተኛውን በየሥራ ክፍሉ በቡድን ተከፋፍሎ የሚያከናውኑበት አሠራር መመቻቸቱን ታውቋል፡፡

 

Cement

 

የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በአገራችን በግንባታው ዘርፍ ማነቆ ሆኖ የሚገኘውን የሲሚንቶ ዋጋ ንረትና የምርት እጥረት ለማረጋጋት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ምርቱን እንደዲያከፋፍሉ ግንቦት 21 ቀን 2012 ዓ/ም በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በተደረሰው ውሳኔ መሠረት ምርቱን ከአገር ውስጥ አምራቾች በመግዛት በኮንስትራክሽን ሥራ ለተሠማሩ አካላት ማከፋፈል ጀምሯል፡፡

 

ኮርፖሬሽኑ የሲሚንቶ ምርትን በቀጥታ ከአምራች ፋብሪካዎች በተለይም በዋነኝነት ከዳንጎቴ፣ ደርባና ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካዎች በመግዛት ለአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት፣ ለጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥትና ለአዲስ አበባ አስተዳደር ለሚገኙ የመንግሥት ፕሮጀክቶች፣ ለክፍለ ከተሞችና በግንባታው ለተሠማሩ ሌሎች አካላት በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡

 

በአገራችን እየተከሰተ ባለው የሲሚንቶ ዋጋ ንረት ምክንያት የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው በከፍተኛ ደረጃ እየተጎዳ እንደሚገኝና ይህንን ለማስተካከል በንግድና ኢንዱስትረ ሚኒስቴርና በሲሚንቶ አምራች ኢንዱስትሪ ባለቤቶች መካከል ውይይቶች ሲደረጉ ቢቀይም ችግሩ ሊፈታ ካለመቻሉ በተጨማሪ በአንዳንድ አካባቢዎች ከፍተኛ የሆነ የሲሚንቶ ምርት እጥረት እየተከሰተ መሆኑን ከንግድ ሚኒስቴር የተገኘው መረጀ ያመለክታል፡፡

 

በመሆኑም ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ከአምራች ፋብሪካዎች፣ ከመንግሥት የልማት ድርጅቶች፣ ከክልሎችና ከከተማ አስተዳደሮች የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊዎች ጋር ባደረገው ውይይት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች የሲሚንቶ ምርትን በቀጥታ ከፋብሪካዎች በመግዛት እንዲያከፋፍሉ፤ አምራች ፋብሪካዎችም የሲሚንቶ ምርታቸውን በቀጥታ ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች እንዲሸጡ በወሰነው መሠረት ነው ኮርፖሬሽኑ የማከፋፈል ሥራውን እየከወነ የሚገኘው፡፡

 

እስከ ሐምሌ 1 ቀን 2012 ድረስ ባለው ጊዜ ከ90 ሺህ በላይ ኩንታል ሲሚንቶ ለምርት ፈላጊዎች መከፋፈሉን ከሽያጭ ክፍሉ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

 

የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን እና የኢፌዴሪ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ በየዘርፈቸው ለሚያከናውኗቸውና የየተቋማቱን የሥራ አፈጻጸም ለማገልበት የሚረዱ መልካም ተሞክሮዎችንና ከምርትና ገበያ ጋር የተያያዙ መረጃዎችን ለመለዋወጥ የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ጥቅምት 11 ቀን 2012 ዓ/ም በኢንሥኮ ዋና መሥሪያ ቤት ተፈራርመዋል፡፡

በስምምነቱ ተቋማቱ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን የግብይት ዋጋዎችን እንዲሁም በመረጃዎች ላይ ተመሥርተው የተሚካሄዱ ጥናትና ጥናቶችንና ትንታኔዎችን ውጤቶች በመለዋወጥ በግብርናው ዘርፍ የሚሰሩ አካላትንና የአምራች አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ መሆኑ በሰነዱ ላይ ተጠቅሷል፡፡

በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በዋነኝነት የአነስተኛ አርሶ አደሮችን የማምረት አቅም ለማጎልበት የሚያስችሉ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ድጋፎችን የማድረግ፣ በመረጃ ትንተና እና ጂአይኤስ ዙሪያ መልካ ተሞክሮዎች ከግብርና ትራንስፎርሜሽን የማግኘት እንዲሁም ከኤጀንሲው ጋር በመሆን የግብርና መረጃጃ አያያዝን የማዘመን ሥራዎችን ማከናወን የሚችልበት ዕድል እንደሚፈጥርለት ተገልጿል፡፡

በተመሣሣይም የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ በመረጃ በመረጃ ላይ የተመሠረቱ ውጤቶችን ለማግኘት የሚያስችሉ ወቅታዊ የመረጃ ግብዓቶችንና በኢንሥኮ የተተገበሩ የመረጃ አያያዝ መልካም ተሞክሮዎችን የሚያገኝባቸውን ስልቶች መተግበር የስምምነቱ አካል መሆናቸው ታውቋል፡፡

አነስተኛ አርሶ አደሮችም በወቅታዊና ትክክለኛ መረጃዎች ላይ ተመስርተው ከሚነደፉ ስትራቴጂዎች፣ ፖሊሲዎችና ፕሮጀክቶች ተጠቃሚ እንደሚሆን በስምምነቱ ሰነዱ ተመልክቷል፡፡

 

 

 

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ አባላት የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሥራ እንቀስቃሴ የሚገመግም ጉብኝት በኮርፖሬሽኑ ዋና መሥሪያ ቤትና በዘርፍ መ/ቤቶች አካሂደዋል፡፡

አባላቱ በቆይታቸው አራቱምን የኮርፖሬሽኑን የሥራ ዘርፎች ወቅታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ያደመጡ ሲሆን በኮርፖሽኑ የፍጆታ ዕቃዎች የንግድ ሥራ ዘርፍ መ/ቤት፣ በሎጂስቲክስ አገልግሎትና በእህልና ቡና የንግድ ዘርፍ የቡና ማደራጃ ማዕከል በመገኘት የሥራ እንቅስቃሴ ጉብኝት አድርገዋል፡፡

በጉብኝቱ ላይ የኮርፖሬሽኑ የሥራ ኃላፊዎች በየዘርፉ እየተከናወኑ ያሉና አገራዊ ጠቀሜታቸው የጎላ ተግባራትን ለአባላቱ ያብራሩ ሲሆን በአንጻሩ የአፈጻጸም ክፍተት የሚታይባቸውንና መንግሥታዊ ድጋፍን የሚሹ ጉዳዮችን በመለየት ለኮሚቴው አቅርበዋል፡፡ በተጨማሪም የቋሚ ኮሚቴው አባላት ከኮርፖሬሽኑ የሠራተኛ ማኅበር ተወካዮች ጋር በመገናኘት መሻሻል በሚገባቸው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው አባላት በጉብኝቱ ማጠቃለያ ላይ ኮርፖሬሽኑ የዋና መ/ቤትና የዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች ጋር አጠቃላይ ውይይት አበረታች ተግባራትን ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በማሳሰብ፣ ኮርፖሬሽኑ ሊያሻሽል ይገባዋል ባሏቸው ጉዳዮች ላይ አቅጣጫዎች በማስቀመጥና በኮርፖሬሽኑ የሥራ አፈጻጸም ላይ ተግዳሮት የሚፈጥሩ ጉዳዮቸን ለመፍታት በሚያስችሉ አካሄዶች ላይ የጋራ ግንዛቤን በመውሰድ የተሻለ ለውጥ ለማምጣት እንደሚሠሩ አስረድተዋል፡፡

Planting01.jpg

ደን ህይወት ነው፡፡ አዎ በእርግጥም ደን ህይወት ነው፡፡ ዓለማችንን እያስጨነቀ ያለው የአየር ንብረት ለውጥ መንስኤው የደን መመናመን ነው፡፡ ምድራችን ያለደን ውበት የላትም፡፡ ደን ስትለብስ ግን ግርማ ሞገሷን ትላበሳለች፤ እስትንፋሷም ይስተካከላል፡፡

 

ዕጽዋት የከተማችንን የአየር ንብረት ለመጠበቅም ሆነ አካባቢን ለማስዋብ ያላቸው ጠቀሜታ የጎላ ከመሆኑ አንጻር ችግኞችን መትከል የተተከሉትን ተንከባክቦ ማሳደግ ለአካባቢ ጥበቃ መሠረት ነው፡፡ በያዝነው በጀት አመት አረንጓዴ አሻራ እናሳርፍ፤ በአንድ ጀምበር 200 ሚሊየን ችግኝ እንትከል!” በሚል መሪ ቃል በመላ ሀገሪቱ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍል ያሳተፈ የችግኝ ተከላ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ መርኃ ግብሩ በዋናነት ሐምሌ 22 ቀን 2011 ዓ/ም የሚከናወን ሲሆን እንቅስቃሴው ቀድሞ ተጀምሯል፡፡ ይህ መርኃ ግብር የሀገሪቱን የደን ሽፋን ትርጉም ባለው መልኩ አንድ እርምጃ ወደ ፊት የሚያራምድ መሆኑ በብዙዎች ተስፋ ተጥሎበታል፡፡

 

የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ይህንን ሀገራዊ አጀንዳ ተቀብለው ሀምሌ 6 ቀን 2011 ዓ/ም ሳሪስ በሚገኘው የኮርፖሬሽኑ የእህል ማከማቻ ቅጥር ግቢ ውስጥ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም አካሂደዋል፡፡

 

በችግኝ ተከላው ወቅት የኮርፖሬሽኑ ኮርፖሬት ሰርቪስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታሪኩ በራሱ መርሃ ግብሩን አስመልክተው ደን ከሰው ልጆች ህይወት ጋር ቀጥተኛ ትስስር ያለውና ከደማችን ጋር የተያያዘ መሆኑን በመጥቀስ ንጹህና ያልተራቆተ አካባቢን ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ ያሳሰቡ ሲሆን ችግኞችን መትክል ብቻ ሳይሆን የተተከሉትም እንዲጸድቁ ተገቢውን እንክብካቤ ማድረግ እንደሚገባ በመጠቆም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

 

ኮርፖሬሽኑ በአካባቢ ጥበቃ ፕሮግራሙ የችግኝ ተከላን በዋና መሥሪያ ቤቱና በክልል የግብይት ማዕከላት የነደፈ ሲሆን የኮርፖሬሽኑ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች የአካባቢ ፕሮግራሙን ተግባራዊ ማድረግ ከጀመሩ ዓመታትን አስቆጥረዋል፡፡

 

ዘንድሮም የተሣተፉት የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በዕለቱ የተተከሉትን ችግኞችም ሆነ የቀደሙትን ተንከባክበው ለፍሬ እንደሚያበቁ በችግኝ ተከላ ፕሮግራሙ ላይ ቃል ገብተዋል፡፡