የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በዋናነት የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን፣ መሠረታዊ ሸቀጦችን ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገር በተወዳዳሪ ዋጋ በመግዛት ለአርሶ አደሩና አምራቹ የገበያ ዕድል ለመፍጠር፤ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን እንዲሁም መሠረታዊ ሸቀጦችን ለሸማቹ ማኅበረሰብ ለመንግሥትና መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማትና ለዱቄት ፋብሪካዎች በመሸጥ ገበያን ለማረጋጋት፤ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ላልሆኑ ተቋማት የውክልና ግዥ ለማካሄድና በግዥ ዙርያ የማማከርና የሥልጠና አገልግሎት ለመስጠት፤ የሀገራችንን ቡና፣ የቅባት እህል፣ ጥራጥሬ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ለውጭ ገበያ በመሸጥ የውጭ ምንዛሪን ለሀገራችን ለማስገኘት የተቋቋመ የፌደራል የመንግሥት የልማት ድርጅት ነው፡፡
የንግድና አገልግሎት ዘርፎች
እህልና ቡናየኢንሥኮ የእህልና ቡና ንግድ ሥራዎች በዋነኝነት የተመረጡ የእህል ምርቶችን ቅባትና እና ጥራጥሬ እህሎች፤ እንዲሁም ቡናን ከአገር ውስጥ አምራቾች በመግዛት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ በማቅረብ አርሶ አደሩ የእህል ማምረት ፍላጎቱን በማሳደግ ገበያ መፍጠር ߹ ለህብረተሰቡንም የእህል ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ግብይቱን የተረጋጋ ያደርጋል፡፡ በዚህም ለሸማቾች ህብረት ስራ ማህበራት ለልዩ ልዩ ተቋማት የግብርና ምርቶች አቅርቦት ይካሄዳል፡፡ለሀገር ውስጥ ገበያ ማረጋጊያ የሚውሉ የምግብ እህሎች• ጤፍ• የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ስንዴ• በቆሎና ገብስከኢትዮጵያ ምርት ገበያ ተገዝተው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ የግብርና ምርቶች- የታጠበ ቡና (የሲዳማ፣ የይርጋጨፌ፣ የነቀምት፣ የሊሙ)- ያልታጠበ ቡና (የሐረር፣ የሲዳማ፣ የጅማ፣ የቴፒ፣ የነቀምት)- የቅባት እህሎች (ነጭ የወለጋና የሁመራ ሰሊጥ፣ ኑግ፣ ተልባ)- ጥራጥሬ (ነጭና ቀይ ቦሎቄ፣ ባቄላ፣ አኩሪ አተር፣ ማሾ፣ ሽምብራ)አቅራቢዎች• የአርሶ አደር ኅብረት ሥራ ማኅበራት• የመንግሥትና የግል አምራቾችየወጪ ንግድ መዳረሻዎችቻይና፣ ፈረንሣይ፣ ኮሪያ፣ እስራኤል፣ አሜሪካ፣ ጅቡቲ፣ ቤልጅየም፣ ዱባይየግብይት ቦታዎችበኮርፖሬሽኑ ዋና መስሪያቤት የውጭ ስንዴ እና ሌሎች የግብርና ምርቶች ሽያጭ የሚከናወን ሲሆን በሁሉም ክልሎች ባሉ 122 ክልሎች ግብይት ማዕከላትና ጣቢያዎች የውጭ ስንዴ እና ሌሎች የግብርና ምርቶች ግብይት ይከናወናል፡፡የግብይት ማዕከላት
አዲስ አበባ ዙሪያ ግብይት ማዕከል --> 0114 16 17 99
አዳማ ግብይት ማዕከል --> 0221 11 11 77
ሻሸመኔ ግብይት ማዕከል --> 0461 10 42 35
ነቀምት ግብይት ማዕከል --> 0576 61 10 17
ደ/ማስቆስ ግብይት ማዕከል --> 0587 71 10 38
ባህር ዳር ግብይት ማዕከል --> 0582 20 01 15
አሰላ ግብይት ማዕከል --> 0223 31 10 78
ደሴ ግብይት ማዕከል --> 0331 11 17 33
ጅማ ግብይት ማዕከል --> 0471 11 09 73
መቀሌ ግብይት ማዕከል --> 0344 41 33 59
ድሬደዋ ግብይት ማዕከል --> 0251 11 20 45
ለመረጃስልክ: +251114167884/68ፋክስ: +251114704373
አትክልትና ፍራፍሬየኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በአትክልትና ፍራፍሬ ንግዱ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን ከአገር ውስጥ አምራቾች በመግዛት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ የሚያቀርብ ሲሆን የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ መሰረታዊ ሸቀጦችን አቅርቦትን በማሳደግ ገበያን በቀጥታ የማረጋጋት እንዲሁም ለሀገራችን ስነ-ምህዳር የሚስማማሙ የተመረጡ የአትክልት ዘሮችን ከወጭ ሀገር አስመጥቶ አምራቾችን ተጠቃሚ የማድረግ ሥራዎችን ያከናውናል፡፡ በተጨማሪም ልዩ ልዩ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን ለውጭ ገበያ ያቀርባል፡፡የምርት ዓይነቶች- ብርቱካን፣ ሙዝ፣ ማንጎ፣ አናናስ፣ ካሮት፣ ሽንኩርት፣ ድንች፣ ቲማቲም፣ ስኳር ድንች፣ መንደሪን፣ ኮምጣጤ፣- የቲማቲም ድልህ፣ የቲማቲም ጭማቂ፣ የብርቱካን ማርማላት፣ ፓስታና ማካሮኒ፣ ሩዝ- የተለያዩ የአትክልት ዘሮች- ዱቄት፣ ስኳርና የምግብ ዘይትአቅራቢዎችአትክልትና ፍራፍሬ አምራች ገበሬዎች፣ እርሻ ልማቶችለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችማንጎ፣ አቮካዶ፣ ቲማቲም፣ ሙዝ፣ ብርቱካን፣ ድንችየወጪ ንግድ መዳረሻዎችጅቡቲ፣ ሶማሊላንድየሽያጭ/ማከፋፈያ መደብሮች- በአዲስ አበባ የሚገኙ የችርቻሮ መሸጫ መደብሮች- በሁሉም ክፍለ ከተሞች በሚገኙ የሽያጭ ኮንቴነሮች የችርቻሮ ሽያጭ ይካሄዳልየማከፋፈያ መደብሮች- ፒያሳ - አትክልት ተራ ጎን- አፍንጮ በር - ስድስት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ አምስተኛ በር አካባቢ- ቄራ - በኢንሥኮ የአትክልትና ፍራፍሬ ንግድ ዘርፍ ዋና መሥሪያ ቤትበክልሎች-በሁሉም ክልሎች በሚገኙ 105 አትክልትና ፍራፍሬ ማከፋፈያ ማዕከላትና የመሸጫ ሱቆች ሽያጭ ይካሄዳልቢሾፍቱ ማከፋፈያ --> 0114/33 83 65
አዳማ ማከፋፈያ --> 0221/11 13 99
መተሃራ ማከፋፈያ --> 0222/26 00 27
ሀረር ማከፋፈያ --> 0226/66 15 30
ድሬደዋ ማከፋፈያ --> 0251/11 21 98
አሰላ ማከፋፈያ --> 0223/31 27 11
ሻሸመኔ ማከፋፈያ --> 0461/10 34 48
ባህር ዳር ማከፋፈያ --> 0582/20 40 93
ሀዋሳ ማከፋፈያ --> 0461/10 34 48
አርባ ምንጭ ማከፋፈያ --> 0114/16 36 65ለመረጃስልክ: +251114164288፣ +251114160338
የፍጆታ ዕቃዎችኢንሥኮ በፍጆታ ዕቃዎች ንግድ ሥራው ምርቶችን ከውስጥና ከውጭ አምራቾች በማቅረብ የገበያ ዋጋን የማረጋጋትና ለሸማቹን በተመጣጣኝ ዋጋ የምርት አቅርቦትን ለማረጋገጥ ይሠራል፡፡ የንግድ ሥርዓቱ የምርት ሰንሰለትም ያጠረ እንዲሆን በማድረግ ጥራቱን የጠበቀ ምርት በአስተማማኝነት በሸማቾች ማህበራት፣ በሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ ካፌዎችና በቸርቻሪዎች በኩል በቀጥታ ለሸማቹ እንዲደርሱ ይደርጋል፡፡የምርት ዓይነቶች- መሠረታዊ የምግብ ሸቀጦች (ዘይት፣ ስኳር፣ የስንዴ ዱቄት)- የታሸጉ ምግቦች- የተለያዩ ለስላሳ መጠጦች- የቤትና የግል ንጽህና መጠበቂያዎች- መቆያና ጣፋጭ ምግቦች- የጽህፈት መሳሪያዎች በተመጣጣኝ ዋጋ በቸርቻሪዎች አማካይነት ለተጠቃሚዎች በመሸጥ የፍጆታ ሸቀጦች ዋጋን ማረጋጋት ነው፡፡የፍጆታ ሸቀጦች ግብይት ማዕከላትበአዲስ አበባ- ቃሊቲ - ደብረ ዘይት መንገድ ቆርኪ ፋብሪካ ፊትለፊት- መገናኛ - ኒያላ ሞተርስ አጠገብ- መርካቶ - የቀድሞው ጅንአድ ግቢ ውስጥበክልሎች- በሀዋሳ - ሃዋሳ ግብርናኮሌጅ በስተጀርባ- በሻሸመኔ - ከኢትዮ ቴሌኮም ፊትለፊት- በደሴ - ደሴ የአውቶቡስ ጣቢያ/ከአምባሰል ንግድ ስራ ጎን- ባህርዳር - ፓፒረስ ሆቴልቃሊቲ ሽያጭ ማዕከል --> 0114 71 70 34
መገናኛ ሽያጭ ማዕከል --> 0116 67 26 34
መርካቶ ሽያጭ ማዕከል --> 0111 26 61 19በክልሎች የሽያጭ መደብሮች አድራሻ
ባህር ዳር ሽያጭ ማዕከል --> 0582 26 66 88
ደሴ ሽያጭ ማዕከል --> 0333 11 00 67
ሀዋሳ ሽያጭ ማዕከል --> 0462 12 32 38
ሻሸመኔሽያጭ ማዕከል --> 0462 11 51 69ለመረጃስልክ: +251114705454+251114716132+251114717834
የግዢና ማማከር አገልግሎትኢንሥኮ በዋናነት በውክልና ግዥ የመፈጸምና በግዥ ዙርያ የማማከርና የሥልጠና አገልግሎቶችን መንግሥታዊና መንግሥታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች ይሰጣል፡፡ የግዥና የማማከር አገልግሎት በመደበኛ ግዥ ለጨረታ አጽዳቂ ኮሚቴ በሚረዱ አሠራሮች፣ በግዥና አቅርቦት ማኔጅመንት፣ በኮንትራት ማቴሪያል ማኔጅመንት እንዲሁም በገቢና ወጪ ንግድ ፕሮሲጀር ስራዎች የሚሰጣቸው ስልጠናዎች በአንድም ሆነ በሌላ በኩል በአገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄዱ ዋና ዋና ሰፋፊና ከፍተኛ የቴክኒክ እውቀት የሚሹ ግዥዎችን እውን በማድረግ የግዥ ሂደቱን ውጤታማ በማድረግ እውቀትን በማሸጋገር በመንግሥት ተቋማት ላይ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን በማስወገድ የፕሮጀክቶች አፈጻጸምን በማቀላጠፍና በሌሎችም መስኮች ችግርን ለመፍታትና ሥራን ለማሳለጥ ሰፊ አስተዋጽኦ አላቸው፡፡ዓመታዊ የሥልጠና መርኃ ግብር
REGULAR PROCUREMENT TRAINING
PROCUREMENT FOR ENDORSING COMMITTEE
CONTRACT MANAGEMENT
PURCHASING & SUPPLIES MANAGEMENT
MATERIALS MANAGEMENT
IMPORT & EXPORT PROCEDURE
LEGAL ASPECTS OF INTERNATIONAL SALES CONTRACT
ለመረጃስልክ: +251 11 440 3613ፋክስ: +251 11 440 3579ተጓዳኝ አገልግሎቶችየኢንዱስትሪ ምርት አቅርቦት
ሲሚንቶ ምርቶችን ለተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያውን እናረጋጋለን!
በተጓዳኝነት የምንሰጣቸው አገልግሎቶች• በዘመናዊ ማሽኖች ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ የቅባት እህልና ጥራጥሬ፣ ቡና ማበጠር እና ማደራጀት አገልግሎት፣
• ዘመናዊ የእህል እና ቡና መጋዘኖች ኪራይ በአዲስ አበባና በሁሉም ክልሎች ባሉ ግብይት ማእከላት ፣
• እስከ 80 ቶን እህልና ቡና የመመዘን አቅም ባላቸው የምድር ሚዛኖች የምዘና አገልግሎት በአዲስ አበባ ፣አዳማ ፣ጅማ ፣ድሬደዋ እና ነቀምት ግብይት ማእከላት ፣
• በዘመናዊ የከባድና ቀላል መኪኖች የእህልና ቡና ጭነት እስከ ወደብ ድረስ ማጓጓዝ፣
• የእህል ህክምና ወይንም እጥነት አገልግሎት (fumigation)፣
• የከባድና ቀላል መኪኖች ጥገና እና የማሽን ሾፕአድራሻ
ለመጋዘኖች ኪራይና የእህል ህክምና
ስልክ: +251 114 42 0594ለተሸከርካሪ ጥገና የማጓጓዝ እና የማሽን ሾፕ አገልግሎት
ስልክ: +251 114 40 2535