ስለ እኛ የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈጻሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን ባወጣው አዋጅ ቁጥር 916/2008 አንቀጽ 5 መሠረት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 369/2008 ታኅሳስ 12 ቀን 2008 ዓ/ም የተቋቋመ የፌዴራል መንግሥት የልማት ድርጅት ነው፡፡ ኮርፖሬሽኑ በተናጠል ሲንቀሳቀሱ የነበሩትን የኢትዮጵያ የእህል ንግድ ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ንግድ ድርጅት፣ የኢትዮጵያ አትክልትና ፍራፍሬ ገበያ አክስዮን ማህበር እና የግዥ አገልግሎት ድርጅትን በማቀፍ በንግዱ ዘርፍ ከተሠማሩ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ በተመሠረተ መደጋገፍና መተባበር በመሥራት የንግድ ግብይት ሥርዓቱን የተረጋጋ፣ ዘመናዊ፣ አስተማማኝና ውጤታማ ለማድረግና ተወዳዳሪ ተቋም ሆኖ ለመገኘት የሚሠራ የመንግሥት የልማት ተቋም ነው፡፡ |
ግንቦት 12 ቀን 2015 ዓም በቀድሞው ግሎባል በአሁኑ የኢትዮጵያ ሆቴል በተካሄደው የምስጋና ዕውቅና መርሃ ግብር ኮርፖሬሽኑ በ2015 ዓ/ም በተካሄደው 8ኛው የካይዘን ዓመታዊ የሽልማት ውድድር በካይዘን ትግበራና ውጤታማነት በአገልግሎት ዘርፍ 3ኛ...
የጃፓን መንግስት ለኢትዮጵያ የ 57ሺ ኩንታል የጃፓን ሩዝ ድጋፍ አደረገ፡፡ የምግብ ድጋፍ ርክክብ ሥነ-ስርዓቱ ግንቦት 08/ 2015 ዓ.ም በኮርፖሬሽኑ የፍጆታ እቃዎች ንግድ ሥራ ዘርፍ ቃሊቲ ሽያጭ ማእከል የተካሄደ ሲሆን የገንዘብ...
አዳዲስና ዘመናዊ አሰራር ለዘረጉ፣ የላቀና ተጨባጭ እድገት ላስመዘገቡ፣ መልካም ስማቸውን ጠብቀው ለአመታት በትጋት ለዘለቁ ተቋማት /MILESTONE, BRANDING AND REPUTATION/ አቢሲኒያ የጥራት ድርጅት እውቅና ለመስጠት ሚያዚያ 1 ቀን 2015 ዓ/ም በኢንተርሊግዠሪ...
ኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከአራቱም ዘርፎችና ከዋና መ/ቤት የተውጣጡ ሴት ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በአንድነት ፓርክ መጋቢት 15 ቀን 2015 ዓ/ም ጉብኝት አካሂደዋል፡፡ ጉብኝቱን ያዘጋጀውና ያስተባበረው የኮርፖሬት...
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በአገራችን ያለውን መሠረታዊ የምግብ ፍጆታ ምርቶች አቅርቦት እጥረትና የዋጋ ንረትን ለመቋቋም የተለያዩ የፍጆታ ምርቶችን በማከፋፈል ገበያውን ማረጋጋት እና የሃገር ውስጥ አምራቾችን ማበረታታት ከተሰጡት ተልዕኮዎች መካከል ተጠቃሽ...
ኮርፖሬሽኑ በ2015 በጀት ዓመት ባለፉት ሰባት ወራት በሀገር ውስጥና በውጭ ገበያ ለመሸጥ ካቀደው 2.29 ሚሊዮን ኩንታል የእህልና ቡና፣ የፍጆታ ዕቃ እና የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርት 2.27 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ወይም...