ስለ እኛ የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈጻሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን ባወጣው አዋጅ ቁጥር 916/2008 አንቀጽ 5 መሠረት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 369/2008 ታኅሳስ 12 ቀን 2008 ዓ/ም የተቋቋመ የፌዴራል መንግሥት የልማት ድርጅት ነው፡፡ ኮርፖሬሽኑ በተናጠል ሲንቀሳቀሱ የነበሩትን የኢትዮጵያ የእህል ንግድ ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ንግድ ድርጅት፣ የኢትዮጵያ አትክልትና ፍራፍሬ ገበያ አክስዮን ማህበር እና የግዥ አገልግሎት ድርጅትን በማቀፍ በንግዱ ዘርፍ ከተሠማሩ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ በተመሠረተ መደጋገፍና መተባበር በመሥራት የንግድ ግብይት ሥርዓቱን የተረጋጋ፣ ዘመናዊ፣ አስተማማኝና ውጤታማ ለማድረግና ተወዳዳሪ ተቋም ሆኖ ለመገኘት የሚሠራ የመንግሥት የልማት ተቋም ነው፡፡
|
![]() |
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በአገራችን ያለውን መሠረታዊ የምግብ ፍጆታ ምርቶች አቅርቦት እጥረትና የዋጋ ንረትን ለመቋቋም የተለያዩ የፍጆታ ምርቶችን በማከፋፈል ገበያውን ማረጋጋት እና የሃገር ውስጥ አምራቾችን ማበረታታት ከተሰጡት ተልዕኮዎች መካከል ተጠቃሽ...
ኮርፖሬሽኑ በ2015 በጀት ዓመት ባለፉት ሰባት ወራት በሀገር ውስጥና በውጭ ገበያ ለመሸጥ ካቀደው 2.29 ሚሊዮን ኩንታል የእህልና ቡና፣ የፍጆታ ዕቃ እና የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርት 2.27 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ወይም...
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርት ጥራቱና ደህንነቱ የተጠበቀ ማድረግ የሚያስችል ማቀዝቀዣ መጋዘንን ጨምሮ ሁለገብ ሕንጻ ለማስጀመር የሚያስችል የመሰረት ድንጋይ ማስቀመጥ ስነ-ስርዓት የካቲት 25/2015 ዓ.ም በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ...
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሚያከናውናቸው የምርት የግብይት ሥራዎች ለማሳለጥ የመያገለገሎ ተጨማሪ አራት ከባድ ተሽከረካሪዎች ግዢ አከናወነ፡፡ የተሸከርካሪ ርክክቡ በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት በተከናወነበት ወቅት አንደተገለጸው የተገዙት ተሸከርካሪዎች እያንዳንዳቸው 50 ኩንታል፣ በድምሩ...
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ከየካቲት 16-20/2015 ዓ.ም "የወጪ ንግድ ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ቃል እያካሄደ ባለው ዓውደ ርዕይ ላይ በመሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡...
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በአገር ውስጥ የሚታየው የዘይት ምርት ዋጋ ንረትና አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ በመንግሥት በተላለፈው ውሳኔ ከተገዛው ውስጥ የ5 ሚሊየን ሊትር የፓልም ዘይት ሥርጭት እያከናወነ ነው፡፡ ጅቡቲ ከሚገኘው ጎልደን...